አንድ መነኩሴ ወደ ገዳሙ አበ ምኔት ቀርቦ በምሬት እንዲህ አለ :- - አትሮንስ ሚዲያ

አትሮንስ ሚዲያ

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Thursday, September 29, 2022

አንድ መነኩሴ ወደ ገዳሙ አበ ምኔት ቀርቦ በምሬት እንዲህ አለ :-

አንድ መነኩሴ ወደ ገዳሙ አበ ምኔት ቀርቦ በምሬት እንዲህ አለ :-
"አባቴ በዚህ ገዳም ምንም ጸጋ ምንም ትሩፋት የሌለኝ መነኩሴ እኔ ብቻ ነኝ:: አባ እገሌን እዩት እንደ እርሱ የዋህ የለም! አባ እገሌን እዩአቸው እንደርሳቸው ታጋሽ ማን አለ? አባ እገሌን እዩአቸው ለሁሉ ፍቅር አላቸው!
እኔ ግን ምንም የለኝም አልረባም አባቴ እባክዎ ይጸልዩልኝ የእኔ ጸጋ የእኔ ፍሬ ምንድር ነው?" አለ እያለቀሰ::
አበምኔቱም አይዞህ ጸልይ ብለው አሰናበቱት::
እሱ ከወጣ በኁዋላ ግን አብረዋቸው ላሉት መነኮሳት እንዲህ አሉ :-
"ይህ መነኩሴ በዚህ ገዳም ካሉ ሁሉ የሚበልጥ ጸጋ ተሠጥቶታል:: የወንድሞቹ ኃጢአት አይታየውም
ጽድቃቸውን ግን በትሕትና ሲቆጥር ይውላል:: ከዚህ በላይ ምን ጸጋ አለ? ዝም ያልኩት ይህንን ብነግረው ክብሩን አሳንስበታለሁ ብዬ ነው" አሉ::
"ነፍሳችሁን ተመልከቱ የወንድማችሁንም ኃጢአት አትመልከቱ እግዚአብሔር ያያል" ቅዳሴ እግዚእ
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሚያዝያ 23 2012 ዓ ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
 

 


No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages