ስለ ፍኖተ ጽድቅ ሚዲያ በመምህር ያረጋል አበጋዝ የተሰጠ መልእክት - አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Thursday, April 24, 2025

ስለ ፍኖተ ጽድቅ ሚዲያ በመምህር ያረጋል አበጋዝ የተሰጠ መልእክት

 





እኔ በበኩሌ ፍኖተ ጽድቅ ሚዲያን እጅግ ዘለግ ባለ ጥርጣሬ እንድመለከተው ሆኛለሁ ። ብጹዕነታቸው አቡነ ገብርኤል በፍኖተ ጽድቅ ሚዲያ ስለ "ጸጋ" ብቻ አይደለም የተሳሳቱት ጥሩ ሌሎች ጉዳዮችም አሉ ።
በእውነቱ ከሆነ በአውደ ምህረት ላይ ቢሆን ይኸንን ያስተምሩ ነበር ወይ !? ብለን ብንጠይቅ አይሞክሩትም ባይ ነኝ ።
ለዚህ የተሳሳተ ትምህርታቸው መቼት ያደረጉት ፍኖተ ጽድቅ ሚዲያን ነው ። ይኸ ደግሞ በአጋጣሚ ሳይሆን ሆን ተብሎ ነው ነኝ ። ፍኖተ ጽድቅ ሚዲያ የገንዘብ ኃይል እንጂ የእግዚአብሔር ኃይል የራቀው ሚዲያ ነው ብለን ለመደምደም ጫፍ ደርሰናል ።
አስተውላችሁ ከሆነ ስለ ጸጋ የተሳሳተ ግንዛቤ ብጹዕነታቸው በሚያስተላልፉበት ወቅት እዚያው በፍኖተ ጽድቅ ሚዲያ የሥራ ድርሻ ያለው ስሙን ለጊዜው የዘነጋውት ጥቁር የሰባኪ ጋዎን የለበሰ ሰው ይስቅ ነበር ።
ሳቁም "ለዘመናት የተከማቸ ተረት የሆነ ትምህርት በብጹዕነታቸው ተደረመሰ" የሚል ተሃድሶአዊ ሳቅ ይመስላል ። ተሃዶሶዎች ሲስቁ እንዲህ ነው የሚስቁት ።
ለማንኛውም ብጹዕ አቡነ ገብርኤል እንወድዎታለን እናከብርዎታለን እኛ (ምዕመናን) የእናንተን ቅንጣት ታክል አቅም ፣ ዕውቀት ፣ ጸጋ እና ትጋት የለንም ። ነገር ግን በእርስዎ ትምህርት ጸረ ቤተ ክርስቲያን አቋማቸውን በየጊዜው የሚያንጸባርቁ ሰዎች በደስታ ሲቦርቁ በተቃራኒው ለዚህች ቤተ ክርስቲያን በኑሮም በዕውቀትም በሁለንተናቸውም ዋጋ የከፈሉ ኦርቶዶክሳዊያን ሲያዝኑ ተመልክተናል ።
ነገሩን ስንመረምረውም እጅግ አደገኛ እና እንኳን አንድ ሊቀ ጳጳስ ይቅርና ጀማሪ ሰባኪ ሊሳሳተው የማይችለውን ስህተት ነው የተሳሳቱት ። የምግባር ስህተት ቢሆን ይኸንን ያክል እርቀት ሄጄ በሊቀ ጳጳስ ላይ ለመጻፍ በፍጹም አልደፍርም ነበር ። ነገሩ ሃይማኖታዊ ሆነና እንዲህ ተዳፍረን ጻፍን ።
ለማንኛውም መምህር ያረጋል አበጋዝ ያሉትን እንስማ ። በነገራችን ላይ ይኸ የመምህር ያረጋል አበጋዝ ግሳጼ የተላለፈው በራሱ በፍኖተ ጽድቅ ሚዲያ እንደሆነ በቪዲዮ ላይ የሚታየው የፍኖተ ጽድቅ ሎጎ ያመለክታል ። ይኸ ጥሩ ጎናችሁ ነው ።

No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages