መጋቢት 7 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
በውይይታቸውም ብፁዕነታቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ሁኔታ ለሊቀ ጳጳሱ በሰፊው አብራርተውላቸዋል።
በተጨማሪም ሀገረ ስብከቱ በጀርመን ለመመሥረት ባስበው ገዳም ዙርያና ይህንኑ አስመልክቶ ቤተ ክርስቲያን በምትፈልገው ዕርዳታ ዙሪያ ገለጻ አድርገውላቸዋል።
በሙንስተር ከተማ ስላለው የመንበረ ንግሥት በዓታ ለማርያም አጥቢያ ጉዳይም ውጤታማ ውይይት አድርገዋል።
በሁሉም ጉዳዮች የብፁዕነታቸውን ማብራሪያ የሰሙት ሊቀ ጳጳስ ዶ/ር ጌንም ጽሕፈት ቤታቸው በሁሉም ጉዳዮች ላይ በተቻለው ዐቅም አብሮ እንደሚሠራ፣ አስተዋጽዖ እንደሚያደርግም ቃል ገብተውላቸዋል።
የሙንስተር ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሀገረ ስብከት በጀርመን ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ከሚገኙት አኅጉረ ስብከት የኮለንን ሀገረ ስብከት ተከትሎ በሁለተኛ ደረጃ ብዙ ካቶሊካውያን የሚገኙበት ሀገረ ስብከት ነው። ዘገባው የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ነው።
ምንጭ፤ ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል
No comments:
Post a Comment