መካነ ቅዱሳን አባ እንጦንስ ሰንበት ትምህርት ቤት ጎንደር - አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Monday, June 1, 2020

መካነ ቅዱሳን አባ እንጦንስ ሰንበት ትምህርት ቤት ጎንደር

🌱ሰንበት ት/ቤት ዘጎንደር🌱
እናስተዋውቃችሁ
🍂የሰ/ት/ቤቱ ሥም :- መካነ ቅዱሳን አባ እንጦንስ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት
🍂ቤተ ክርስቲያኑ የታነጸበት ጊዜ:-በፃድቁ ዮሐንስ ዘመን /ከ1660-1674ዓ.ም/ ሲሆን ከጎንደር አርባ አራቱ ታቦታት አንዱ ነው፡፡ በቀሃ ወንዝ ሙላት ምክንያት ቢቋረጥም ለበርካታ ዓመታት የጎንደር መንበረ ጵጵስ በመሆን አገልግሏል፡፡፡፡
🍂ዓመታዊ ክብረ በዓል፦ ጥር 22 የጻድቁ እረፍታችና ሐምሌ 22 ቅዳሴ ቤታቸው ይከበራል፡፡
🍂ሰ/ት/ቤቱ የተመሠረተው ጊዜ :- ጥቅምት 2010 ዓ/ም
🍂መገኛ ሀገረ ስብከት :- በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በጎንደር ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት
🍂የቤተ ክርስቲያኑ አድራሻ፤ ዞብል ክ/ከተማ አባ እንጦንስ የገጠር ቀበሌ ቀሃ ወንዝ ማዶ
🍂የሰ/ት/ቤቱ የጉባዔ አከፋፈል፤ የህፃናትና የአዋቂዎች/የወጣቶች/
፩/የህፃናት ጉባኤ መርሐ ግብሮች-
➡️መደበኛ ጉባዔ መርሐ ግብር ቅዳሜ 4:00-6:00
፪/ የአዋቂዎች መርሐ ግብር
➡️መደበኛ ጉባዔ መርሐ ግብር እሁድ 8:00-10:30
🍂በደብሩ የሚገኝ የአብነት ት/ቤት
➡️ቅዳሴ ትምህርት ቤት፣
🍂ደብሩ አዋሳኞች
➡️በስተምስራቅ ጎንደሮች ጊዮርጊስ ቤ/ን
➡️በምዕራብ ወራንገብ ጊዮርጊስ ቤ/ን
➡️በሰሜን የቁልቋልየ ማርያም ቤ/ን
➡️በደቡብ ቀሃ ኢየሱስና ቁስቋም ማርያም ቤ/ን
🍂ከሰ/ት/ቤቱ አርያአነት ያለው ተሞክሮ ፤
ቤተ ክርስቲያኑ ምንም አይነት ገቢ የሌለውና ሰንበት ት/ቤቱም የአገልግሎት መፈጸሚያ ቁሳቁስም ሆነ አዳራሽ የሌለውም ቢሆን፣ እንዲሁም ቦታውም ከጎንደር ወጣ ያለ በወንዝ የተከበበም ቢሆን የሰንበት ት/ቤቱ ጉባዔ ሳይፈታ መከናወኑ ጥሩ ተሞክሮ ነው፡፡
🍂ስለ ሰንበት ት/ቤቱ አድራሻ
📲የሰ/ት/ቤቱ ሰብሳቢ ተስፋሁን ማንደፍሮ 0925176168 ወይም 0962091536
🥀በመጨረሻም፦ሰንበት ት/ቤቱ ምንም አይነት አገልግሎት መፈጸሚያ ግብዓት እንኳን የሌለው በመሆኑ/መማሪያ አዳራሽ፣ አልባሳት፣ ከበሮ፣ ጸናጽል፣ መቋሚያ፣መጽሐፍ ቅዱስ፣ቅዱሳት መጻሕፍት ወ.ዘ.ተ/ በተጠቀሰው የሰንበት ት/ቤት ሰብሳቢ ስልክ ወይም በአካል በመቅረብ ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ፡፡
ይቆየን!!

No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages