ቅዱስ ሲኖዶስ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የቀጣይ ዓመት መደበኛ በጀት 7.1 ቢሊዮን ብር አጸደቀ። ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ - አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Thursday, July 9, 2026

ቅዱስ ሲኖዶስ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የቀጣይ ዓመት መደበኛ በጀት 7.1 ቢሊዮን ብር አጸደቀ። ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ቅዱስ ሲኖዶስ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የቀጣይ ዓመት መደበኛ በጀት 7.1 ቢሊዮን ብር አጸደቀ። ኢኦተቤ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ግንቦት ፬ ቀን ​፳፻፲፰ ዓ.ም የ፳፻፲፰ ዓ.ም ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው አምስተኛ ቀን ስብሰባ በአራት አጅንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በዕለታዊ መግለጫው አሳውቋል። ከነዚህ መካከልም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የቀጣይ ዓመት የበጀት ዕቅድ አንዱ ነው። በመሆኑም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይቤተ ክህነት ጽ/ቤት ለ2019 ዓ·ም በጀት ዓመት ገቢና ወጪ ሒሳብ አስመልክቶ ከበጀትና ሒሳብ መምሪያ የተዘጋጀ ዓመታዊ መደበኛ የበጀት ዕቅድ 46 ገጽ የተመለከተ ሲሆን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከበጀትና ሒሳብ መምሪያ የተዘጋጀውን ዓመታዊ የበጀት ዕቅድ በንባብ አዳምጦና ከጉባኤው በቀረቡት ጥያቄዎች የባለሙያዎችን ምላሽ ከሰማ በኋላ በጉዳዩ ላይ በስፋት ተነጋግሮ የሚከተለውን ውሳኔ አሳልፏል፡፡ በውሳኔውም መሠረት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ያቀረበው የ2019 ዓ·ም በጀት ዓመት ከነመጠባበቂያው ብር7,101,018,660.16 (ሰባት ቢሊየን አንድ መቶ አንድ ሚሊየን አሥራ ስምንት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ብር ከአሥራ ስድስት ሣንቲም) በበጀት ዓመቱ የበጀት አርዕስቱን ጠብቆ በሥራ ላይ እንዲውል የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መወሰኑን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል (ረ/ፕ) ለ EOTCTV በሰጡት ዕለታዊ ማብራሪያ አስታውቀዋል ። ምንጭ፡ © EOTC t.v.

No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages