ቤተክርስቲያንን ለተኩላ ተላልፋ በአደባባይ አሳልፈው ሰጧት - ወልደ ሥላሴ ኪዳኔ - አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Saturday, July 25, 2026

ቤተክርስቲያንን ለተኩላ ተላልፋ በአደባባይ አሳልፈው ሰጧት - ወልደ ሥላሴ ኪዳኔ


አዝናለሁ። በጣም አዝናለሁ። ነውርንና ብልግናን reinforce በሚያደርግ ሥርዓት ውስጥ በመኖሬ። ቤተክርስቲያንን ለተኩላ ተላልፋ በአደባባይ አሳልፈው ሰጧት። ፖለቲካ እና ገንዘብ ብቻ ሥራ በሚሰራበት ዘመን ይህንን እያየሁ በመኖሬ አዝናለሁ።
አንዳንዱ ክህነቱ ተይዞ ምዕመን ሆኖ መኖር (ለእሱም ከበቃ) ሲኖርበት የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ሆኖ ሲመጣ ስመለከት አዝናለሁ። የሚገርመው ደግሞ ሰውየው ያሰማራው ዲጂታል ሰራዊት የውዳሴ ዶፍ እያወረዱለት ነው። የገጽታ ግንባታ መሆኑ ነው።
አየር ጤና መካነ ስብሐት ቅዱስ ሩፋኤልና ቅድስት ልደታ ቤተክርስቲያን አጥቢያዬ ነው። የማስቀድስበት፣ኪዳን ማደርስበት፣በየለቱ የምሳለመው ደብሬ። ፍልሰታን ተረጋግቼ እዚሁ ላሳልፍ አስቤ ነበር። ይህን ሰውዬ እያየሁ ግን የምችል አይመስለኝም። ሌላ ደብር ሔደን እናሳልፋለን። ለእኛ ለምዕመናን ይህ ትልቅ ፈተና ነው። ትልቅ የመሰናክል ድንጋይ ነው። የከተማ መነኩሴ ቤተክርስቲያንን ሊያጠፋት ነው። ከገንዘብና ከፖለቲካ ንክኪ በቀር ቤተክርስቲያንን ማያውቁ ወሮበላዎች እጅ ወደቀች። ይህን መታገል የልጅነት ግዴታችን ነው።
 ምንጭ፤ ወልደ ሥላሴ ኪዳኔ (ፌስ ቡክ)



No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages