ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ለአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ። EOTCMK TV ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም - አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Thursday, July 9, 2026

ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ለአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ። EOTCMK TV ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም

ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ለአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ። EOTCMK TV ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የባሕር ዳር እና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ስልጠናውን በአባታዊ መመሪያና ቡራኬ በከፈቱበት ወቅት ስልጠናው አዲስ እውቀት የሚማሩበት ብቻ ሳይሆን ከአሁን በፊት ያገኙትን መሠረታዊ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትምህርትና ሥርዓት መሠረት ያደረገ አስተደደራዊ ክህሎትን ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል። ብፁዕነታቸው በተጨማሪም ለሰልጣኞች ባስተላለፉት መልእክት ቅዱስ ጳውሎስ ለቲቶ የጻፈለትን መልእክት በማስታወስ አስተዳዳሪዎች በመልካም ሥራቸው ለሌሎች አርዓያና ምሳሌ መሆን እንዳለባቸው አጽንዖት ሰጥተው አሳስበዋል። ስልጠናው ከሐምሌ 1 ጀምሮ ለአንድ ወር የሚቆይ መሆኑን ከሀገረ ስብከቱ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል የተገኘው መረጃ ያሳያል።

No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages