ህያውን ከሙታን መካከል ለምን ትፈልጋላችሁ? - አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Saturday, April 18, 2020

ህያውን ከሙታን መካከል ለምን ትፈልጋላችሁ?


 

 ህያውን ከሙታን መካከል ለምን ትፈልጋላችሁ?
እንደተናገረ ተነስቷል


እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላምና በፍቅር
አደረሳችሁ፤ አደረሰን።


የዓለማት ሁሉ ፈጣሪ : የዘለዓለም አምላክ ወልድ
ዋሕድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህች ዕለት መግነዝፍቱልኝ  መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በባሕርይ ኃይሉና ሥልጣኑ ተነስቷልና እንኳን ደስ አለን:: 

ከዚህ በኋላ ለ፶ ቀናት እንዲህ እያልን ሰላምታ እንለዋወጣለን:- 

ክርስቶስ ተንስአ እሙታን፣

በዐቢይ ኃይል ወስልጣን፣

አሠሮ ለሰይጣን፣

አግዐዞ ለአዳም፣ 

ሰላም፣

እምይእዜሰ
ኮነ፣ 

ፍሥሐ ወሰላም!

በእርግጥም አምላካችን በሞቱ ሞትን ገድሎ በትንሣኤው ሕይወትን አድሎናልና ደስታ ይገባናል:: መድኃኔ ዓለም በኅቱም ድንግልና እንደ ተወለደ በኅቱም መቃብር ተነስቷል::
ለደቀ መዛሙርቱም "ሰላም ለእናንተ ይሁን" ሲል በዝግ ደጅ ገብቷል::
በዕለተ ትንሣኤው የመጀመሪያውን ደስታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተካፍላለች:: የእርሷን ያህል በሃዘን የተጐዳ የለምና:: ቀጥለው ቅዱሳት አንስት እነ ማርያም መግደላዊት
ትንሣኤውን አይተዋል:: ሰብከዋልም::
በዚች ቀን ማዘን አይገባም:: በትንሣኤው
የደነገጡና የታወኩ የአጋንንትና የአይሁድ ወገኖች ብቻ ናቸውና::አምላካችን ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ከትንሣኤው በረከት አይለየን:: በዓሉንም የሰላም : የፍቅርና የበረከት ያድርግልን:: የጌታችን በጐ ምሕረቱ በሁላችን ትደርብን::
"ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም:: 'የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ
አልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል: በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው' እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደተናገረ አስቡ::"
(ሉቃ. ፳፬፥፭-፰) "አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነስቷል:: ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኗልና:: ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና::"
(፩ቆሮ. ፲፭፥፳)

ወስብሐት ለእግዚአብሔ

No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages