(መስከረም 11 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ)
የአዲስ አበባ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ እንዲሁም የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የቦርድ ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ሥር የሚገኘው የአስኮ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል በዘመናዊ መልኩ ለሚያሠራው አዲስ ቤተልሔም የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።
ብፁዕነታቸው ከመሠረት ድንጋይ ማስቀመጥ በኋላ ባደረጉት ንግግር የቤተክርስቲያን ዋና ተግባር መንፈሳዊ አገልግሎትን ማሳለጥ ቢሆንም ልማታዊ ሥራዎችን ማከናወንም የሚመከር ነው ብለዋል።
አክለውም በዛሬው ዕለት የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጥንለት ቤተልሔም በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ሲሉ አባታዊ መመሪያ አስተላልፈዋል።
በመርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅን ጨምሮ የብፁዕነታቸው ፕሮቶኮል ሊቀ ጉባኤ አባ ኃይሉ እንዳለ፣ የትምህርትና ሥልጠና ዋና ክፍል ኃላፊ መ/ም በቃሉ ወርቅነህ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ብሉይ ፈቃደ ፣ የደብሩ ሊቃውንት እና ሰ/ት/ቤት አባላት ተገኝተዋል።
Post Top Ad
Wednesday, September 21, 2022

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ አስኮ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ለሚያሠራው አዲስ ቤተልሔም የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ!!
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
Post Bottom Ad
Author Details
Templatesyard is a blogger resources site is a provider of high quality blogger template with premium looking layout and robust design. The main mission of templatesyard is to provide the best quality blogger templates which are professionally designed and perfectlly seo optimized to deliver best result for your blog.
No comments:
Post a Comment