ቤተ ክርስቲያን በ26 ግለሰቦች ላይ ክስ እንድትመሠርት ውሳኔ ሰጥቷል። - አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Thursday, March 9, 2023

ቤተ ክርስቲያን በ26 ግለሰቦች ላይ ክስ እንድትመሠርት ውሳኔ ሰጥቷል።


 

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሁለተኛ መሠረታዊ መብቶችና ነጻነቶች ችሎት ቤተ ክርስቲያን እስከ ከመጋቢት 18 ቀን 2015 ዓ.ም በሕገ ወጡ ሹመት ላይ በተሳተፉ 26 ግለሰቦች ላይ ክስ እንድትመሠርት ውሳኔ ሰጥቷል።

በዛሬው ዕለት የቤተ ክርስቲያኗ የሕግ ክፍል በተሰጠ መግለጫ እንደተገለጸው ግለሰቦቹ ወደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት እንዳይገቡ፣ ንብረቷን እንዳይወስዱ፣ ዓርማና ስም እንዳይጠቀሙ የሚከለክለውም እግድ እስከ ተጠቀሰው ቀን ይቀጥላል ተብሏል።
የሕገ ወጦቹ ተሿሚዎች ጠበቃዎች በዕለቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ሰውነት የላትም የመክሰስ ሥልጣን የላትም፤ ልትከስሰን አትችልም፤ ሃይማኖታዊ ጉዳይ ስለሆነ ፍርድ ቤት እጁን ሊያስገባ አይገባም። በፍርድ ቤት ሊታይ አይገባም፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን "ተዋሕዶ" የሚለውን ስም መጠቀም አትችልም፤ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንን ወክላ መክሰስ አትችልም በማለት የክስ መቃወሚያ ቢያቀርቡም ፍርድ ቤቱ ውድቅ ማድረጉን በመግለጫው ተገልጿል።
ሕገ ወጡ ሹመት ላይ የተሳተፉ ግለሰቦች እግድን እየተላለፉ እንደሚገኙ በመግለጽ የፍርድ ቤቱን ትእዛዝና እግድ መተላለፍ በወንጀል ተጠያቂ እንደሚያደርግ አስገንዝበዋል።
ይህንን እንዲያስፈጽሙ የታዘዙ ተቋማት በአለማስፈጸማቸው ተቋማቱንም ጭምር ተጠያቂ እንደሚያደርግ እና አፈጻጸሙ ፍርድ ቤቱ ነገ በሚሰጠው አቅጣጫ መሠረት እንደሚወሰን በመግለጫው ተጠቅሷል።

source: ©EOTC TV
ለተጨማሪ መረጃ የሀገረ ስብከቱ ማኅበራዊ ድረ-ገጾችን ይጎብኙ:-
1. ድረ-ገጽ:- www.addisababa.eotc.org.et

No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages