የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በተፈፀመው የአበው መነኮሳት ግድያ የተሰማትን ሀዘን ገለፀች ! - አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Tuesday, February 27, 2024

የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በተፈፀመው የአበው መነኮሳት ግድያ የተሰማትን ሀዘን ገለፀች !



የካቲት 17 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
++++
የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በተፈፀመው የአበው መነኮሳት ግድያ የተሰማትን ሀዘን በቤተ ክርስቲያኒቷ የውጭ ግንኙነት መምሪያ አማካይነት ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ባስተላለፉት መልእክት ሀዘናቸውን ገልፀዋል።
መልእክቱ በኦሮሚያ ክልል በዝቋላ አቦ ጥንታዊ ገዳም በወንድሞቻችን ላይ በተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል።
የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለቅዱስነታቸው አቡነ ማትያስ በላከችው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥንታዊ ገዳም ላይ በደረሰው አሰቃቂ ጉዳት የተሰማትን ጥልቅ ሀዘን ገልጻለች። የሩሲያ ቤተ ክርስቲያን የውጭ ግንኙነት መምሪያ ሊቀ መንበር ሜትሮፖሊታን አንቶኒ የወንጀሉን አስከፊነት በአጽንኦት ገልጸው፣ ይህም ከመለኮታዊም ሆነ ከሰው ሕግ ጋር የሚቃረን መሆኑን ተናግረዋል።
ዘገባውን ለማጠናቀር
- የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የውጭ ግንኙነት መምሪያ ድረ ገጽ እና
- ኦርቶዶክሲ ኮግኔት ፔጅን ተጠቅመናል።

No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages