መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች - አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Saturday, October 22, 2022

መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች

 

መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች

የቤተ ክርስቲያኒቷ መሰረታዊ ተልእኮ  ለሰው ልጆች መንፈሳዊና ማህበራዊ አገልግሎቶችን መስጠት ነው ለዚህም ነው የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ. ለዘመናት ያለምንም የሃይማኖት፣ የዘር፣ የፆታ ልዮነት ከህዝቦች ሁሉ ጋር ተቀራርባ በመሥራት ሰብዓዊ ተግባራትን የሞትፈፅመው የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ለማህበራዊና የኢኮኖሚያዊ ልማት መስፋፋት የራሷን ልዩ አስተዋፅኦ በማድረግ የሀገሪቱን ልማት የምታለማና የምትደግፍ ብሔራዊት ቤ/ክ ናት፡፡

የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ. የትምህርት ታሪክ እንደሚያስረዳን ቤተ ክርስቲኒቷ የትምህርታዊ ሥነጽሑፍ ሥርዓት ምንጭ እንደሆነች ያስረዳል ይህም የቤተ ክርስቲያኒቱ ትምህርታዊ አገልግሎት በኢትዮጵያ የግዕዝ ፊደላትን ፣ የቀን መቁጠሪዎችና ቋንቋዎችን ከመቅረፃና ከማሳደግ ጀምራል፤ የታረክ ቅርሶች፣ የጥናትና ምርመር ሊቃውንት እንዲያሚረጋግጡት በኢትዮጵያ የጽሕፈት ሥራ የተጀመረው
ከክርስቶስ ልደት ከ1000 ዓመት በፊት ጀምሮ ነው፡፡ በመሆኑም የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ. የፅህፈት ሥራ ላይ ያዋለችው እምነቷን ማስፋፋት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ነው፡፡ስለሆነም የግዕዝ ቋንቋና ፊደላት በአክሱም ዘመነ መንግስት የበላይነትን እያገኙ በሀውልቶችና በሌሎች ነገሮች የሚጻፉ ጽሑፎች በግዕዝ ቋንቋና ፊደላት በመጠቀም የትምህርት ሥርዓቷን ማሳደግ ችላለች፡፡

የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ከተመሰረተችበት ጊዜ ጀምሮ በህዝቦቿ ሃይማኖታዊ፣ ማህበራዊና ትምህርታዊ ህይወት ውስጥ ታላቅ ድርሻ አበርክታለች እያበረከተችም ትገናለች፡፡ የጥንቱ ትምህርት መለያ ባህሪ ያገኘው ልዩ ከሆነው ከሀገሪቱ ክርስቲያናዊ ውርስ ነው ክርስትና በተሰፋፋባቸው የኢትዮጵያ ደጋማ አካባቢዎች ቤተ ክርስቲያኒቷ ዋናውን የኢትዮጵያን ጥንታዊ ባህል መሥርታለች ከዚህም የተነሳ ለብዙ መቶ ዓመታት ጥንታውያን ትምህርት ቤቶችን ማቋቋምና ማስፋፋት ችላለች የቤተ ክርስቲያን የትምህርት ሥርዓት የኢትዮጵያን ጥንታዊ ትምህርት ጠብቆ ለማቆየት አገልግሏል ለትውልድም ሊተላለፍ የቻለው በዚህ ሥርዓት አማካንነት ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን የትምህርት ሥርዓት የሚከተሉት ዋና ክፍሎች አሏት እነርሱም፡-

  1. ንባብ ቤት
  2. ቅዳሴ ቤት
  3. ዜማ ቤት
  4. ቅኔ ቤት
  5. መጽሐፍ ቤት ናቸው

መንፈሳዊ ዜማ ቤት

የቤ/ክ መዝሙር በሰፊው የሚሰጥበት ት/ቤት ዜማ ቤት በመባል ታወቃል፡፡ ዜማ ማለት በግዕዝ፤በዕዝልና በዓራራይ የሚገር ከሰማየ ሰማያት የተገኘ መንፈሳዊ የመላእክት መስጋና ማለት  ነው፡፡ይህም ግዕዝ በአብ፤ዕዝል በወልድ እና ዓራራይ በመንፈስ ቅዱስ የሚመሰል ነው፡፡ በታወቀው የዜማ ደራሲ በቅዱስ ያሬድ እንደተደረሱ የሚነገርላቸው የተለያዩ የዜማ ዓይነቶች አሉ ከእነዚህም መካከል አንዱና ዋናው ድጓ ነው፡፡

ቅዳሴ ቤት

ይህ ት/ቤት ዲያቆናትና ቀሳውስት የቅዳሴን ዜማ በጥልቀት የሚማሩበት ት/ቤት ነው የቅዳሴ ትምህርት ሰደድኩላና ደብረ ዓባይ በሚል በ2 የዜማ ዓይነቶች ተከፍሎ የሚሰጥ ነው፡፡

ቅኔ ቤት

በዚህ ት/ቤት ተማሪዎች በግዕዝ ቋንቋ  ግጥምችን እንዲገጥሙ ት/ት ይሰጣቸዋል፡፡ ቅኔ ፣ የዜማና የግጥም ምጣኔ ያለው በእንግሊዝኛ ናፖይትሪን ከተሰኘው ቃል ጋር ተመሳሳይነት ያለው ነው በቅኔ ቤት ተማሪዎች የሚማሩት የቅኔ ግጥም መግጠም ብቻ ሳይሆን የግዕዝ ቋንቋን ከሰዋሰዋዊ ህግጋቱ ጋር ነው በመሆኑም ቅኔ ማጥናት /መማር የግዕዝን ሥነ ጽሑፍ ለመረዳት ዋና ቁልፍ ነው፡፡

መጽሐፍ ቤት

ይህ ትምህርት ቤት የብሉይና የሐዲስ የመፃሕፍተ ሊቃውንትና የመፃህፍተ መነኮሳት ትርጓሜ የሚሰጥበት ትምህርት ቤት ነው፡፡በዚህ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የቤተክርስቲያንን ትውፊት፣ ዶግማ፣ታሪክና ሕገ ቤተ ክርስቲያንን በእያንዳንዱ ትርጓሜ አማካኝነት ይማራሉ፡፡

የቤተክርስቲያን ት/ቤቶች ጠቀሜታና አስፈላጊነት እስከ 19ኛ መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ የቤተ ክርስቲያኒቱ ትምህርት ቤቶች በሀገሪቱ ውስጥ ለማበራዊም ሆነ ለመንፈሳዊ ትምህርት ብቸኞች የትምህርት ተቋማት ሆነው አገልግለዋል ቀሳውስቱና የሀገሪቱ ሚኒስትሮች  የእነዚህ ት/ቤት ተቋማት ውጤቶች ነበሩ፡፡ የሕግ ባለሙያዎች፣ ዳኞች፣ ወታደራዊ መኮንኖች፣ ጸሐፊዎች ወዘተ ሥልጠና የሚያገኙት ከእነዚህ ት/ቤቶች ወይማ ገዳማት ነበር በአጠቃላይ ከዚህ መረዳት የምንችለው የቤት ክርስቲኒቱ ት/ቤቶች ለሃይማኖታዊ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን  ለማህበራዊ፣ ህጋዊ ፣ ፖለቲካዊና ባህላዊ አገልግሎቶች እጅግ በጣም አስፈላጊዎች እንደነበሩና እንደ ሆኑም ነው፡፡ በመሆኑም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚያስተዳድራቸው ገዳማትና አድባራት የታወቁ የቅዳሴ፣ ቅኔ፣ የአቋቋም፣ የድጓና የመጽሐፍ መምህራን መድቦ የመማር ማስተማሩ ሂደት በተሳካ ሁኔታ ትምህርትን በመስጠት ላይ ገኛል፡፡

 Source:

አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት/Addis Ababa Diocese

No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages