በመካነ ስብሐት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የ 2.1 ቢሊየን ብር የራስ- አገዝ ሁለገብ ህንፃ የግንባታ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ። - አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Tuesday, June 13, 2023

በመካነ ስብሐት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የ 2.1 ቢሊየን ብር የራስ- አገዝ ሁለገብ ህንፃ የግንባታ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።

ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ)

በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ስር የሚገኘው የመካነ ስብሐት ልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን 2.1 ቢሊየን ብር የራስ- አገዝ ሁለገብ ህንፃ የግንባታ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ አስቀምጧል።
ህንፃው የሚያርፈው በ3,200 ካሬ ሜትር ላይ ሲሆን አጠቃላይ የቦታው ስፋት ደግሞ 25 ሺህ 805 ካሬ ሜትር ነው። የሚገነባው ህንፃ የገበያ ማዕከልና ዓፀደ ህፃናት ትምህርት ቤት መሆኑ ተገልጿል ።
የመሰረት ድንጋይ ያስቀመጡት የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ በኵረ ትጉሃን ዘርዓ ዳዊት ኃይሉ እና የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሃይ በጋራ በመሆን ነው ።
የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ በኵረ ትጉሃን ዘርዓ ዳዊት ኃይሉ እንደገለጹት የሚገነባው ህንፃ መካነ ሰብሐት ልደታ ቤተክርስቲያን ቦታ ላይ ይሁን እንጂ የሚገነባው ግን ለአጠቅላይ የጎንደር ህዝብ አገልግሎት ነው ብለዋል።
የሚገነባው ህንፃ ዓመታትን ማስቆጠር የለበትም ያሉት በኵረ ትጉሃን ዘርዓ ዳዊት በኢትዮጵያ ውሰጥና በመላው ዓለም ያሉ የማኅበረሰብ አንቂዎች እግዚአብሔር በሰጣቸው ጸጋ ተጠቅመው እንዲደግፉና እንዲያስተባብሩ በታሪካዊቷ ጎንደር ሀገረ ስብከት ስም ጥሪ አስተላፈዋል ።
የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሃይ በበኩላቸው ቤተክርስቲያን ለሰላም ግንባታና ለትውልድ ግንባታ እንዲሁም በኪነ ህንጻ አሁን ለደረስንበትና ለምንኮራባቸው ህንፃዎች ያላት አበርክቶ ላቅ ያለ መሆኑን ገልጸዋል ።

ምንጭ፡ ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል




No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages