እናታችን ክርስቶስ ሰምራ - አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

አትሮንስ ሚዲያ - Atrons Media

ስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት ማቴ 16፤15


በቅርብ የተጻፉ

Post Top Ad

Sunday, May 24, 2020

እናታችን ክርስቶስ ሰምራ



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
“የእግዚአብሔር ዓይኖች ወደ ጻድቃን ጆሮቹም ወደ ጩኸታቸው ናቸውና …. ጻድቃን ጮኹ፥ እግዚአብሔርም ሰማቸው ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው……የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፥ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል።” መዝ.፴፫፡-፲፱
የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ፀጋ በረከትዋ ይደርብን።

ሀገሯ ቡልጋ ጽላልሽ ቅዱስጌ ነው። አባቷ ደርበኒ እናቷ እሌኒ ይባላሉ። ለአካለ መጠን ስትደር ሠምረ ጊዮርጊስ ለሚባል ደግ ካህን ዳሯት። ፲፪ ልጆችም ወልዳለታለች። ንጉስ አጼ ገብረ መስቀል የልቧን ቅንነት የምግባሯን ደግነት የምትለብሰው የምታነጥፈው አልባሳት ወርቅ ወጥተው ወርደው የሚያገለግሏት መቶ ሰባ አራት አገልጋዮች ሠደውላታል። በኋላ ዓለምን ንቃ ልብሰ ምንኩስናን አዘጋጅታ ስትሔድ ሕጻን ልጇን ይዛ ኖሮ ልጇ ከዚህ አይገባም ቢሏት ከበር ትታው ገብታለች። ቅዱስ መካኤል ነጥቆ ሄሮድስ ካስፈጃቸው ፲፬ እልፍ ሕጻን ደምሮታል። እሷን በክንፉ ተሸክሞ ታና ሐይቅ አድርሷታል።
“ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ፥ ስለ ሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ?” ዮሐ.፫፡፲፪ በዚህ ከመከራዋ ብዛት ከገድሏ ጽናት ሰውነቷ ተበሳስቶ የዓሣ መመላለሻ እስኪሆን ድረስ ከባሕሩ ገብታ ወደ ግራ ቀኝ ሳትል አሥራ ሁለት ዓመት ጸልያለች። በመጨራሻም ጌታ ምን አደርግልሽ ዘንድ ትሽያለሽ? አላት። እሷም ሰው ሆኖ የማይበድል እንጨትሆኖ የማይጨስ የለምና ውሉደ አዳም እንዳይስቱ ዲያብሎስን ማርልኝ አለችው። ከሆነልሽማ አንጪው አላት ቅዱስ ሚካኤል ወስዶ ሲዖል አደረሳት። ዲያብሎስ ና ውጣ አለችው። በምድር ፈልጌ ባጣሽ ሳዝን ነበር። አሁንማ ከቤቴ መጣሽልኝ ብሎ ጎትቶ አስገባት። ቅዱስ ሚካኤል ተከትሎ ገብቶ ነጥቆ አውጥተቷተታል። ስተወጠጣ ስለ ገድሏ ጽናት ስድስት ክንፍ ተሰጥቷት በዚያ ነፍሳትን ማርካ ወጥታለች። 

በፍጻሜ ዘመኗ በቁመቷ ልክ በዓት ሰርታ ከግራ ከቀኝ ከፊት ከኋላ ዐሥራ ሁለት ጦር ተክላ ወዲያ ወዲህ ሳትል፤ ቆማ ፲፪ አመት ኖራለች። ስትሰግድም ሥጋዋ በጦር ተወግቶና ተፈቅቶ አልቋል። ጌታም ይህን ሁሉ መከራዋን እንደመሥዋዕት ቆጥሮላት በቃል ኪዳኗ የተማጸነውን ስሟን የተራውን እስከ አሥር ትውልድ እንዲምርላት ተስፋዋን ነግሯት ክብርት ነፍሷን ከሥጋዋ ለይቶ በቃለ አቅርንት በዝማሜ መላእክት አሳርጓታል። የዕረፍቷ መታሰቢያ ነሐሴ ፳፬ ይከበራል። በረከቷ አማላጅነቷ፤ ቃል ኪዳኗ አይለየን አሜን።
“እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።” ወደ ዕብ.፲፪፡፩¬-፪ 
(12:-1-2)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለ ወላዲቱ ድንግል ወለ መስቀሉ ክቡር አሜን ይቆየን።

No comments:

Post a Comment

Post Bottom Ad

Pages